In NewsJuly 24, 20231 Minute

የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ከተባበሩት መንግስታት የፕሮጀክት አገልግሎት ቢሮ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራመ

የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ኢ/ር አይሻ መሀመድ በዛሬው ዕለት ከተባበሩት መንግስታት የፕሮጀክት አገልግሎት ቢሮ ዋና ዳይሬክተርና በአፍሪካ ህብረት የ UNOPs ተወካይ ወ/ሮ ወርቅነሽ መኮንን ጋር ሚኒስቴሩ በሚያከናውናቸው የመስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት አቅም ግንባታ ላይ በጋራ ለመስራት ስምምምነት ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱ በኢትዮጵያ ቆላማ አካባቢዎች ያለውን ከፍተኛ የመልማት አቅምና ያልተነካ የተፈጥሮ ሃብት ለመጠቀም እንዲሁም በመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ዙሪያ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል፡፡